113 - Al-Falaq ()

|

(1) በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ፡፡

(2) «ከፈጠረው ፍጡር ሁሉ ክፋት፡፡

(3) «ከሌሊትም ክፋት ባጨለመ ጊዜ፤

(4) «በተቋጠሩ (ክሮች) ላይ ተፊዎች ከኾኑት (ደጋሚ) ሴቶችም ክፋት፡፡

(5) «ከምቀኛም ክፋት በተመቀኘ ጊዜ፤ (እጠበቃለሁ በል)፡፡»