(1) 1. በሰማዩ እና ሌሊት በሚመጣውም እምላለሁ።
(2) 2. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሌሊት መጪው ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?
(3) 3. ጨለማውን ሰንጣቂ ኮከብ ነው::
(4) 4. ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጂ ሌላ አይደለችም::
(5) 5. የሰው ልጅ ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፤
(6) 6. ከተስፈንጣሪ ውሃ (የዘር ፈሳሽ) ተፈጠረ::
(7) 7. ከጀርባና ከእርግብግቢቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ የዘር ፈሳሽ ውሃ (ተፈጠረ)።
(8) 8. አላህ እርሱን በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው::
(9) 9. ሚስጥሮች በሚገለጹበት ቀን፤
(10) 10. (ለሰው) ምንም ኃይልና ረዳት አይኖረዉም::
(11) 11. የመመለስ ባለቤት (ዝናባማ) በሆነችው ሰማይ እምላለሁ::
(12) 12. (በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በሆነችው ምድርም እምላለሁ::
(13) 13. እርሱ (ቁርኣን)፤ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ (የአላህ) ቃል ነው።
(14) 14. እርሱም ቀልድ አይደለም።
(15) 15. እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ያሴራሉ (ይሸርባሉ)::
(16) 16. እኔ ተንኮልንም እመልሳለሁ (አመክናለሁ)::
(17) 17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከሓዲያንን ቀን ሰጣቸው:: ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው (ታገሳቸው)::