86 - At-Taariq ()

|

(1) 1. በሰማዩ እና ሌሊት በሚመጣውም እምላለሁ።

(2) 2. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሌሊት መጪው ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?

(3) 3. ጨለማውን ሰንጣቂ ኮከብ ነው::

(4) 4. ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጂ ሌላ አይደለችም::

(5) 5. የሰው ልጅ ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፤

(6) 6. ከተስፈንጣሪ ውሃ (የዘር ፈሳሽ) ተፈጠረ::

(7) 7. ከጀርባና ከእርግብግቢቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ የዘር ፈሳሽ ውሃ (ተፈጠረ)

(8) 8. አላህ እርሱን በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው::

(9) 9. ሚስጥሮች በሚገለጹበት ቀን፤

(10) 10. (ለሰው) ምንም ኃይልና ረዳት አይኖረዉም::

(11) 11. የመመለስ ባለቤት (ዝናባማ) በሆነችው ሰማይ እምላለሁ::

(12) 12. (በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በሆነችው ምድርም እምላለሁ::

(13) 13. እርሱ (ቁርኣን)(እውነትን ከውሸት) የሚለይ (የአላህ) ቃል ነው።

(14) 14. እርሱም ቀልድ አይደለም።

(15) 15. እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ያሴራሉ (ይሸርባሉ)::

(16) 16. እኔ ተንኮልንም እመልሳለሁ (አመክናለሁ)::

(17) 17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከሓዲያንን ቀን ሰጣቸው:: ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው (ታገሳቸው)::