37 - As-Saaffaat ()

|

(1) 1. መሰለፍን በሚሰለፉት፤

(2) 2. (ደመና) መንዳትን በሚነዱት፤

(3) 3. ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ::

(4) 4. አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ብቻ ነው::

(5) 5. እርሱ ያ በሰማያትና በምድር በመካካለቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው:: የምስራቆችም ጌታ ነው::

(6) 6. እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት (አስዋብናት)::

(7) 7. አመጸኛ ከሆነ ሰይጣንም ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት::

(8) 8. ወደ ላይኛው ሰራዊት አያደምጡም፤ ከየአቅጣጫውም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፤ (ይቀጠቀጣሉ)

(9) 9. የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፤ ለእነርሱም ዘውታሪ ቅጣት አለባቸው::

(10) 10. ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውኑም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር (እርሱ ይሰማዋል)::

(11) 11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ ከእነርሱ በፊት የፈጠረነው ፍጡር? እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው::

(12) 12. ይልቁንም ማስተባበላቸው አስደነቀህ፤ በመደነቅህም ይሳለቃሉ::

(13) 13. በተገሰጹም ጊዜ አይገሰጹም::

(14) 14. ተዓምርንም ባዩ ጊዜ ለመሳለቅ ይጣጣራሉ።

(15) 15. አሉም: «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።

(16) 16. «በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በሆን ጊዜ የምንቀስቀስ ነን?

(17) 17. «የቀድሞዎቹ አባቶቻችንም እንደዚሁ ይቀሰቀሳሉን?» (ይላሉ።)

(18) 18. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «አዎን! እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)።» በላቸው።

(19) 19. እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት:: እነርሱም ወዲያውኑ ምን እንደሚፈጸምባቸው ያያሉ::

(20) 20. «ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው።» (ይላሉም)

(21) 21. «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉት የነበራችት መለያው ቀን ነው።» ይባላሉ።

(22) 22. (ለመላዕክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ከአላህ ሌላ ይገዟቸው የነበሩትንም ጣዖታት በአንድ ሰብስቡ።

(23) 23. ከአላህ ውጭ (ይገዟቸው የነበሩትን ሰብስቡ)። ከዚያም ወደ ገሀነም መንገድ ምሯቸው።

(24) 24. «እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና አቁሟቸዉም።» (ይባላል።)

(25) 25. ለነርሱም «ምን ሆናችሁ ነው የማትረዳዱት?» ይባላሉ።

(26) 26. በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ማምለጫ የሌላቸው ወራዳዎች ናቸው::

(27) 27. እርስ በራሳቸውም የሚወቃቀሱም ሆነው ይመጣሉ።

(28) 28. (ተከታዮቹ ለአስከታዮቻቸው) «እናንተ በጉልበት ትመጡብን ነበር» ይላሉ።

(29) 29. (አስከታዮቹም) ይላሉ፡- «አይደለም ፈጽሞ አማኞች አልነበራችሁም።

(30) 30. «ለእኛም በናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም። በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ህዝቦች ነበራችሁና ነው እንጂ።

(31) 31. «በእኛም ላይ የጌታችን ቃል የተረጋገጠብንና ሁላችንም ቅጣቱን ቀማሽ ነን።

(32) 32. «እኛ ጠማሞች ስለ ነበርን ወደ ጥመት ጠራናችሁም።» ይላሉ።

(33) 33. ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው::

(34) 34. እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሰራለን።

(35) 35. እነርሱ «ከአላህ ሌላ ትክክለኛ አምላክ የለም» በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ።

(36) 36. «እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን እንዴ?» ይሉ ነበር።

(37) 37. አይደለም እውነቱን ሃይማኖት አመጣ፤ መልዕክተኞቹንም እውነተኝነታቸውን አረጋገጠ።

(38) 38. እናንተ አሳማሚውን ቅጣት እርግጥ ቀማሾች ናችሁ::

(39) 39. ትሰሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም::

(40) 40. ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ቅጣትን አይቀምሱም::

(41) 41. እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አለላቸው::

(42) 42. ፍራፋሬዎች (አሉላቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው::

(43) 43. በድሎት ገነቶች ውስጥ::

(44) 44. ፊት ለፊት የሚተያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ ይንፈላሰሳሉ::

(45) 45. ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዙ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል::

(46) 46. ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከሆነች፤

(47) 47. በእርሷ ውስጥም የራስ ምታት የለባትም:: እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም::

(48) 48. እነርሱ ዘንድ ዓይናቸውን በባሎቻቸው ላይ ብቻ አሳጣሪዎች የሆኑ ዓይናማ ሴቶች አሉ::

(49) 49. እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) እንቁላል ይመስላሉ::

(50) 50. የሚጠያያቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ::

(51) 51. ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ (እንዲህ) ይላል: «እኔ ጓደኛ ነበረኝ።

(52) 52. (እንዲህ) የሚል: ‹በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን?

(53) 53. ‹በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆነ ጊዜ እኛ በእርግጥ እኛ እንመረመራለን?› የሚልም።

(54) 54. እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል::

(55) 55. ይመለከታልም በገሀነም መካከልም ጓደኛውን ያየዋል::

(56) 56. ይላል «በአላህ እምላለሁ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር።

(57) 57. «የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር።» (ይላል)

(58) 58. (የገነት ሰዎች ይላሉ)«እኛ የምንሞት ሰዎች አይደለንምን?»

(59) 59. «የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር እኛም የምንቀጣ አይደለንም» ይላሉ።

(60) 60.ይህ ለገነት ሰዎች የተወሳው እርሱ በእርግጥ ታላቅ እድል ነው::

(61) 61. ለዚህ ብጤ ሰሪዎች ሁሉ ይስሩ::

(62) 62. በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?

(63) 63. እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል።

(64) 64. እርሷ ከገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፤

(65) 65. እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል::

(66) 66. እነርሱ ከእርሷ በይዎች ናቸው:: ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው::

(67) 67. ከዚያ ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅልን መጠጥ አላቸው።

(68) 68. ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው::

(69) 69. እነርሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋል።

(70) 70. እነርሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና።

(71) 71. ከእነርሱም በፊት የነበሩት የቀድሞዎቹ ህዝቦች አብዛሀኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል::

(72) 72. በውስጣቸዉም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል::

(73) 73. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት!

(74) 74. ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ::

(75) 75. ኑህም በእርግጥ ጠራን:: ምንኛ ያማርን ምላሽ ሰጪ ነን?

(76) 76. እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን::

(77) 77. ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን::

(78) 78. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካምን ዝና ተውን::

(79) 79. «በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑህ ላይ ይሁን።»

(80) 80. እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን::

(81) 81. እርሱ ከአማኞች ባሮቻችን ነውና::

(82) 82. ከዚያም ሌሎችን አሰመጥን::

(83) 83. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! ) ኢብራሂምም በእርግጥ ከወገኖቹ አንዱ ነው።

(84) 84. ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ የሆነውን (አስታውስ)::

(85) 85. ለአባቱና ለህዝቦቹ ባለ ጊዜ: «ምንን ትገዛላችሁ?

(86) 86. «ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?

(87) 87. «በዓለማቱ ጌታስ ሀሳባችሁ ምንድ ነው?።»

(88) 88. በከዋክብት መመልከትን ተመለከተ::

(89) 89. እኔ «በሽተኛ ነኝ» አለ።

(90) 90. እነርሱም ከእርሱ የሸሹ ሆነው ሄዱ።

(91) 91. ከዚያ እሱ ወደ አማልዕክቶቻቸው ተዘነበለ፤ (እንዲህ) አለም፡- «አትበሉም እንዴ?

(92) 92. «ምንም የማትናገሩበትስ ምን ምክኒያት አላችሁ?»

(93) 93. በቀኝ (እጁ) የሚመታቸዉም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ::

(94) 94. ወደ እርሱም ሰዎቹ እየሮጡ መጡ።

(95) 95. አለ: «የምትጠርቡትን ትገዛላችሁን?

(96) 96. «አላህ እናንተንም ሆነ የምትሰሩትን ሁሉ የፈጠረ ሲሆን» አላቸው።

(97) 97. «ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም።» አሉ።

(98) 98. ለእርሱ ተንኮልን አስቡ ወራዶችም አደረግናቸው።

(99) 99. አለም፡- «እኔ ወደ ጌታየ ሂያጅ ነኝ፤ በእርግጥ ይመራኛልና።

(100) 100. «ጌታየ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ።»

(101) 101. ታጋሽም በሆነ ልጅም አበሰርነው።

(102) 102. ከእርሱ ጋርም (ለስራ) በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በህልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፤ ተመልከትም፤ ምን ትላለህ?» አለው። «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ስራ፤ አላህ ቢሻ ከታጋሾች ሆኜ ታገኘኛለህ።» አለ።

(103) 103. ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)::

(104) 104. ጠራነዉም: «ኢብራሂም ሆይ!

(105) 105. «ራዕዩን በርግጥ እውን አደረግክ።» እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን።

(106) 106. ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው::

(107) 107. በታላቅ እርድም መስዕዋት ቤዛ አደረግንለት።

(108) 108. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት::

(109) 109. ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን::

(110) 110. ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን::

(111) 111. እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው::

(112) 112. በኢስሐቅም አበሰርነው። ከመልካሞች የሆነ ነብይ ሲሆን::

(113) 113. በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን። ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሰሪ አለ:: ነፍሱን በግልጽ በዳይም አለ::

(114) 114. በሙሳና በሀሩን ላይ በእርግጥ ለገስን::

(115) 115. እነርሱንም ሆነ ህዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን::

(116) 116. ረዳናቸውናም እነርሱ አሸናፊዎቹ ሆኑ::

(117) 117. በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው::

(118) 118. ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው::

(119) 119. በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካምን ዝናን ተውንላቸው::

(120) 120. ሰላም በሙሳና በሀሩን ላይ ይሁን::

(121) 121. እኛ ልክ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን::

(122) 122. ሁለቱም በትክክል በአላህ ካመኑት ባሮቻችን ናቸው::

(123) 123. ኢልያስም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው።

(124) 124. ለህዝቦቹም ባለ ጊዜ (አስታውስ) «አላህን አትፈሩምን?

(125) 125. «ስዕልን ትገዛላችሁ? ከስዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነዉም አምላክ ትተዋላችሁን?

(126) 126. «አላህ ጌታችሁና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁንም ጌታ ትተዋላችሁን?»

(127) 127. አስተባበሉትም ስለዚህ እነርሱ ለቅጣት የሚጣዱ ናቸው::

(128) 128. ንጹህ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ::

(129) 129. በእነርሱ ላይም በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት::

(130) 130. ሰላም በኢልያስ ላይ ይሁን፤

(131) 131. እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን::

(132) 132. እርሱ በእርግጥ ከምዕመናን ባሮቻችን ነው::

(133) 133. ሉጥም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው::

(134) 134. እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳናቸው ጊዜ (የሆነዉን አስታውስ)::

(135) 135. በቅጣቱ ውስጥ ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር::

(136) 136. ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን::

(137) 137. (መኮች ሆይ)፤ እናንተም በእነርሱ መኖሪያዎች ላይ ያነጋችሁ ስትሆኑ ታልፋላችሁ።

(138) 138. በሌሊትም ታልፋላችሁ:: ልብ አታደርጉምን?

(139) 139. ዩኑስም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው።

(140) 140. ወደ ተሞላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ አስታውስ::

(141) 141. እጣም ተጣጣለ፤ ከተሸነፉትም ሆነ::

(142) 142. እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳ ነባሪው ዋጠው::

(143) 143. እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነ ኖሮ

(144) 144. እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር::

(145) 145. እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው ባህር ዳርቻ ላይ ጣልነዉም::

(146) 146. በእርሱም ላይ በአጠገቡ ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን::

(147) 147. ወደ መቶ ሺህ ሰዎችም ላክነው፤ ከቶውንም ይጨምራሉ::

(148) 148. አመኑም። እስከ ጊዜው ድረስም አጣቀምናቸው::

(149) 149. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የመካን ሰዎች ጠይቃቸዉም: «ለጌታህ ሴት ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራሉን?

(150) 150. «ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላዕክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?»

(151) 151. አስተውሉ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው የተነሳ ይላሉ:

(152) 152.፡- «አላህ መላዕክትን ወለደ።» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው።

(153) 153. በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጠን?

(154) 154. ለእናንተ ምን አስረጂ አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!

(155) 155. አትገነዘቡምን?

(156) 156. ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጂ አላችሁን?

(157) 157. «እውነተኞች እንደሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» በላቸው።

(158) 158. በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ:: አጋንንትም ሆኑ ይህን ባዩች በእሳት የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ አውቀዋል::

(159) 159. አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ::

(160) 160. ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች በአላህ ላይ አይዋሹም::

(161) 161. (ካሐዲያን ሆይ!) እናንተም የምትገዟቸዉም ሁሉ፤

(162) 162. በእርሱ በአላህ ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም

(163) 163. ያንን እርሱ ገሀነም ገቢ የሆነውን ቢሆን እንጂ (አጥማሚዎች አይደላችሁም)

(164) 164. (መላእክቶችም አሉ)? «ከእኛ አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ።

(165) 165. «እኛም ጌታን ለመገዛት ተሰላፊዎቹ እኛ ነን።

(166) 166. «እኛም አላህን አጥሪዎቹ እኛው ነን።»

(167) 167. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነርሱ (ከሓዲያን) በእርግጥ ይሉ ነበር:

(168) 168. «ከቀድሞዎቹ መጽሐፍ ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረ ኖሮ

(169) 169. «የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር።»

(170) 170. ግን ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ በእርሱ ላይ ካዱ። ወደ ፊትም በእርግጥ ያውቃሉ::

(171) 171. የእርዳታ ቃላችንም መልዕክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች::

(172) 172. እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ብቻ ናቸው::

(173) 173. ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው::

(174) 174. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከእነርሱም ከመካ ከሓዲያን እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር ተዋቸው::

(175) 175. ተመልከታቸዉም ወደፊትም የሚደርስባቸውን ያያሉ::

(176) 176. በቅጣታችንም ያቻኩሉናልን?

(177) 177. በቀያቸዉም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!

(178) 178. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነርሱን እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ተዋቸው::

(179) 179. ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ::

(180) 180. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ::

(181) 181. በመልዕክተኞቹም ላይ ሰላም ይሁን::

(182) 182. ምስጋና ሁሉም ለዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ ብቻ ይገባው::