(1) 1. አሊፍ ፤ላም ፤ሚይም፤ ራ፤ (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነዚህ አናቅጽ ከመጽሐፉ አናቅጽ ናቸው:: ያም ከጌታህ ወደ አንተ የተወረደው እውነት ነው:: ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያምኑም::
(2) 2. አላህ ያ ሰማያትን የምታይዋት ቋሚዎች ሳይኖራት በችሎታው ከፍ ያረጋት፤ ከዚያ በዐርሹ ላይ ከፍ ያለ፤ ጸሐይንና ጨረቃንም የገራ ነው:: ሁሉም ለተወሰነ ጊዜ ይሮጣሉ:: ነገሩን ሁሉ ያስተናብራል:: ከጌታችሁ ጋር መገናኘትን ታረጋግጡ ዘንድ ተዓምራትን ይዘረዝራል::
(3) 3. እርሱ (አላህ)ያ ምድርን የዘረጋ፤ በእርሷም ውስጥ ተራራዎችንና ወንዞችን ያደረገ:: በውስጧም ከፍሬዎች ሁሉ ሁለት ሁለት ዓይነቶችን ያደረገ ነው:: ሌሊትን በቀን ይሸፍናል:: በዚህም ውስጥ ለሚያስተነትኑ ህዝቦች ሁሉ ብዙ ምልክቶች አሉ::
(4) 4. በምድርም ውስጥ የተጎራበቱ ቁርጥራጮች አሉ:: የወይኖች አትክልቶችም፤ አዝርዕቶችም መንታዎችና መንታዎች ያልሆኑ ዘንባባዎችም አሉ:: በአንድ ውሃ ይጠጣሉ:: በጣዕም ግን ይለያያሉ ከፊልዋንም በከፊሉ ላይ በሚበላው ሰብል እናበልጣለን:: በዚህም ውስጥ ለሚያውቁ ሕዝቦች ሁሉ ብዙ ተአምራት አለበት::
(5) 5. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ብትደነቅም አፈር በሆንን ጊዜ እኛ አዲስ ፍጥረት እንሆናለን? ማለታቸው በጣም የሚደንቅ ነው:: እነዚህ እነዚያ ሰዎች ማለት እነዚያ በጌታቸው የካዱት ሰዎች ናቸው:: እነዚህም እንዛዝላዎች በአንገቶቻቸው ላይ ያሉባቸው ናቸው:: እነዚህም የእሳት ጓዶች ናቸው:: እነርሱ በውስጧ ዘውታሪዎች ናቸው::
(6) 6. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከእነርሱ በፊት የመሰሎቻቸው ቅጣቶች በእርግጥ ያለፉ ሲሆኑ ከመልካሙ በፊት በመጥፎ ያስቸኩሉሃል! ጌታህም ለሰዎች ሁሉ ከመበደላቸው ጋር በእርግጥ የምህረት ባለቤት ነው:: ጌታህ በእርግጥ ቅጣተ ብርቱም ነው::
(7) 7. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነዚያ በአላህ የካዱት ሰዎች «በእርሱ ላይ ከጌታው ተአምር ለምን አልተወረደለትም?» ይላሉ:: አንተ አስፈራሪ ብቻ ነህ፤ ለሕዝብም ሁሉ መሪ አለላቸው።
(8) 8. አላህ ሴት ሁሉ የምታረግዘውን ጽንስ ሁሉ ጠንቅቆ ያውቃል:: ማሕጸኖች የሚያጎድሉትንም ሆነ የሚጨምሩትን ያውቃል:: ነገሩ ሁሉ እርሱ ዘንድ በልክ የተወሰነ ነውና::
(9) 9. ሩቁንና ቅርቡን አዋቂ የሆነ ታላቅና የላቀ ጌታ ነው::
(10) 10. ከናንተ ውስጥ ቃሉን ዝቅ ያደረገ፤ በእርሱ የጮኸም፤ እርሱ በሌሊት ተደባቂም በቀን ተገልፆ ሂያጅም የሆነ ሁሉ (እርሱ አላህ ዘንድ) እኩል ነው (አላህ ያውቀዋል)።
(11) 11. ለእርሱ ለሰው በስተፊቱም ከኋላዉም በአላህ ትዕዛዝ ከክፉ የሚጠብቁት ተተካኪዎች መላዕክት አሉት:: አላህ በሕዝቦች ዘንድ ያለውን (ጸጋ) በነፍሶቻቸው ያለውን (ሁኔታ) እስከሚለውጡ ድረስ አይለውጥም:: አላህም በሰዎች ላይ ክፉን በሻ ጊዜ ለእርሱ መመለስ የለዉም:: ለእነርሱም ከእርሱ ሌላ ምንም ተከላካይ የላቸዉም::
(12) 12. እርሱ ያ የምትፈሩና የምትከጅሉም ስትሆኑ ብልጭታን የሚያሳያችሁ ከባዶች ደመናዎችንም የሚያስገኝ ነው::
(13) 13. ነጎድጓድም አላህን በማመስገን ያጠራል:: መላዕክትም እርሱን ከመፍራት ያጠሩታል፤ መብረቆችም ይልካል። እነርሱም (ከሓዲያን) በአላህ የሚከራከሩ ሲሆኑ በእርሷ የሚሻውን ሰው ይመታል:: እርሱም ሀይለ ብርቱ ነው::
(14) 14. ለእርሱ(አላህ) የእውነት ጥሪ አለው:: እነዚያ ከእርሱ ሌላ የሚገዟቸው ጣዖታት ምሳሌው ወደ አፉ ይደርስ ዘንድ ወደ ውሃ መዳፎቹን በሩቅ ሆኖ እንደሚዘረጋና እንደማይደርስባት ሰው እንጂ ለእነርሱ በምንም አይመልሱላቸዉም:: እርሱም ወደ አፉ ደራሽ አይደለም:: የከሓዲያን ጥሪ በከንቱ ልፋት እንጂ ሌላ አይደለም።
(15) 15. በሰማያትና በምድር ያሉት ሁሉ በዉድም ሆነ በግድ ለአላህ ይሰግዳሉ:: ጥላዎቻቸዉም በጧቶችና በማታዎች ይሰግዳሉ:: (1)
(1) እዚህ አንድ ሱጁድ ይደረጋል። የቁርኣን ንባብ ሱጁድ (ሱጁዱትላዋህ) ይባላል። በቁርኣን ውስጥ 15 ቦታዎች ይገኛል።
(16) 16. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «የሰማያትና የምድር ጌታ ማን ነው?» በላቸው:: «አላህ ነው።» በልም። «ለነፍሶቻቸው ጥቅምንም ጉዳትን የማይችሉን ረዳቶች ከእርሱ ሌላ ያዛችሁን?» በላቸው። «እውርና የሚያይ ይስተካከላሉን? ወይስ ጨለማዎችና ብርሃን ይስተካከላሉን? ወይስ ለአላህ እንደ እርሱ አፈጣጠር የፈጠሩን ተጋሪዎች አረጉለትና ፍጥረቱ በእነርሱ ላይ ተመሳሰለባቸውን?» በልም። «አላህ ሁለመናውን ፈጣሪ ነው:: እርሱም ብቸኛውና ሁሉን አሸናፊው ነው።» በል።
(17) 17. ከሰማይ ውሃን አወረደ:: ሸለቆዎቹም በየመጠናቸው ፈሰሱ:: ጎርፉም አስፋሪውን የውሃ አረፋ ተሸከመ:: ለጌጥ ወይም ለዕቃ ፍላጎት በእርሱ ላይ እሳት የሚያነዱበትም ማዕድን ብጤው የሆነ ኮረፋት አለው:: ልክ እንደዚሁ አላህ ለእውነትና ለውሸት ምሳሌን ያደርጋል:: የውሃ አረፋዉም ግብስብስ ሆኖ ይጠፋል:: ለሰዎች የሚጠቅመውማ በምድር ላይ ይቆያል:: ልክ እንደዚሁ አላህ ምሳሌዎችን ይገልጻል::
(18) 18. ለእነዚያ ለጌታቸው ለታዘዙት ሰዎች መልካም ነገር ገነት አለላቸው:: እነዚያም ለእርሱ ያልታዘዙት ለእነርሱ በምድር ያለው ሁሉ ከእርሱም ጋር ብጤው ቢኖራቸው ኖሮ በእርሱ በተበዡበት ነበር:: እነዚያ ለእነርሱ ክፉ ምርመራ አለባቸው:: መኖሪያቸዉም ገሀነም ናት:: ፍራሻቸዉም ገሀነም ከፋች!
(19) 19. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከጌታህ ወደ አንተ የተወረደው ሁሉ እውነት መሆኑን የሚያውቅ ሰው ልክ እንደዚያ እርሱ እውር እንደ ሆነው ሰው ነውን? የሚገሠጹት የአእምሮ ባለቤቶች ብቻ ናቸው::
(20) 20. እነዚያ የአላህን ቃል ኪዳን የሚሞሉ የጠበቀውንም ኪዳን የማያፈርሱ ናቸው::
(21) 21. እነዚያም አላህ እንዲቀጠል በእርሱ ያዘዘውን ነገር የሚቀጥሉ፤ ጌታቸውንም የሚያከብሩ፤ መጥፎንም ቁጥጥር የሚፈሩ ናቸው::
(22) 22. እነዚያም የጌታቸውን ውዴታ ለመፈለግ የታገሱ ሶላትንም አዘውትረው የሰገዱ ሰዎች እኛ ከሰጠናቸው ሲሳይም በምስጢርም ሆነ በግልጽ የመጸወቱ ክፉውንም በበጎ የሚገፈትሩ ናቸው:: እነዚያ ለእነርሱ መጨረሻይቱ ምስጉን አገር አለችላቸው::
(23) 23. እርሷም የመኖሪያ ገነቶች ናት:: ይገቡባታል:: ከአባቶቻቸዉም ከሚስቶቻቸዉም ከዝርያቸዉም መልካም የሠራ ሰው ሁሉ ይገባባታል። መላዕክትም በእነርሱ ላይ ከየደጃፉ ሁሉ ይገባሉ።
(24) 24. «ሰላም ለእናንተ ይሁን:: ይህ ምንዳ በመታገሳችሁ የተሰጣችሁ ነው:: የመጨረሻይቱም ሀገር ምን ታምር!» ይሏቸዋል::
(25) 25. እነዚያ የአላህን ቃል ኪዳን ከጠበቀ በኋላ የሚያፈርሱ፤ አላህም እንዲቀጠል በእርሱ ያዘዘውን ነገር የሚቆርጡ፤ በምድርም ላይ የሚያበላሹ እነዚያ ለእነርሱ እርግማን አለባቸው:: ለእነርሱም መጥፎ ሀገር ገሀነም አለላቸው::
(26) 26. አላህ ለሚሻው ሁሉ ሲሳይን ያሰፋል:: ለሚሻውም ያጠባል:: ከሓዲያን በቅርቢቱም ሕይወት ተደሰቱ:: የቅርቢቱም ሕይወት ከመጨረሻይቱ አንጻር ትንሽ መጠቀሚያ እንጂ ምንም አይደለችም::
(27) 27. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነዚያም በአላህ የካዱት ሰዎች «በእርሱ ላይ ከጌታው ተዓምር ለምን አልተወረደልትም?» ይላሉ:: «አላህ የሚሻውን ሰው ያጠማል:: የተመለሰንም ሰው ወደ እርሱ ይመራል።» በላቸው::
(28) 28. እነርሱም እነዚያ በአላህ ያመኑ ልቦቻቸዉም አላህን በማውሳት የሚረኩ ናቸው:: አስተውሉ:: አላህን በማውሳት ልቦች ይረካሉ::
(29) 29. እነዚያ በአላህ ያመኑና መልካም ስራዎችን የሠሩት ለእነርሱ ደግ ኑሮና መልካም መመለሻ አለላቸው::
(30) 30. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ልክ እንደዚሁ ከበፊትዋ ብዙ ሕዝቦች በእርግጥ ያለፉ ወደ ሆነችው ሕዝብ እነርሱ በአር-ረህማን የሚክዱ ሲሆኑ ያንን ወደ አንተ ያወረድነውን ቁርኣን በእነርሱ ላይ ታነብላቸው ዘንድ ላክንህ:: «እርሱ አር-ረህማን ጌታዬ ነው:: ከእርሱ ሌላ ትክክለኛ አምላክ የለም:: በእርሱ ላይ ተመካሁ። መመለሻዬም ወደ እርሱ ብቻ ነው።» በላቸው::
(31) 31. ቁርኣንም በእርሱ ተራራዎች የሚነዱበት፤ ወይም በእርሱ ምድር የሚቆራረጥበት፤ ወይም በእርሱ ሙታን እንዲናገሩ የሚደረጉበት ቢሆን ኖሮ (ይሀው ቁርአን በሆነ ነበር።) በእውነቱ ነገሩ ሁሉ የአላህ ነው:: እነዚያ በአላህ ያመኑት ሰዎች እነሆ አላህ በሻ ኖሮ ሰዎችን በመላ በእርግጥ ወደ ቀናው መንገድ ይመራቸው እንደ ነበረ አያውቁምን? እነዚያን የካዱት በሥራቸው ምክንያት አጥፊ አደጋ የምታገኛቸው ከመሆን ወይም የአላህ ቀጠሮ እስኪ መጣ በሀገራቸው አቅራቢያ አንተ የምትሰፍርባቸው ከመሆን አይወገዱም:: አላህ ቀጠሮውን አያፈርስምና::
(32) 32. ካንተ በፊት የነበሩትም መልዕክተኞች በእርግጥ ተላግጦባቸው ነበር:: እናም ለእነዚያም ለካዱት ጊዜን ሰጠኋቸው:: ከዚያም በቅጣት ያዝኳቸው:: ቅጣቴ እንዴት ነበር (ምን ያህል የከፋ ነበር።)
(33) 33. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ነፍስ ሁሉ በሰራችው ሥራ ላይ ተጠባባቂ የሆነው አላህም እንደዚህ እንዳልሆነው ጣዖት ብጤ ነውን? ለአላህ ተጋሪዎችን አደረጉ። «ጥሯቸው:: አላህን በምድር ውስጥ የማያውቀው ነገር ኖሮ ትነግሩታለችሁን? ወይስ ከቃል በቀጥታ ፍቺ በሌለው ከንቱ ቃል ተጋሪዎቹ በማለት ትጠሯቸዋላችሁን?» በላቸው። በእውነቱ ለእነዚያ ለካዱት ተንኮላቸው ተሸለመላቸው። ከእውነቱ መንገድም ታገዱ። አላህ ያጠመመውንም ምንም አቅኚ የለዉም።
(34) 34. ለእነርሱ በቅርቢቱ ሕይወት ቅጣት አለባቸው:: የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት በጣም የበረታ ነው:: ለእነርሱ ከአላህ ቅጣት ምንም ጠባቂ የላቸዉም::
(35) 35. ያች ጥንቁቆች የተሰጧት ገነት ምጣኔዋ (ምሳሌዋ) እንደሚነገራችሁ ነው:: ከሥርዋ ወንዞች ይፈሳሉ:: ምግቧ ሁል ጊዜም የማያቋረጥ ነው:: ጥላዋም እንደዚሁ። ይህች ገነት የእነዚያ የተጠነቀቁት መጨረሻ ናት:: የከሓዲያን መጨረሻ ግን እሳት ናት::
(36) 36. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነዚያም መጽሐፉን የሰጠናቸውን ወደ አንተ በተወረደው ይደሰታሉ:: ከአህዛብም ከፊሉን የሚክዱ ሰዎች አሉ። «እኔ የታዘዝኩት አላህን ብቻ እንድገዛና በእርሱም እንዳላጋራ ነው። ወደ እርሱ እጠራለሁ:: መመለሻዬም ወደ እርሱ ብቻ ነው።» በላቸው።
(37) 37. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ልክ እንደዚሁ በዐረብኛ የተነገረ ፍትህ ሲሆን አወረድነው:: እውቀቱ ከመጣልህም በኋላ ዝንባሌዎቻቸውን ብትከተል ከአላህ ቅጣት ወዳጅም ሆነ ጠባቂ ምንም የለህም::37. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ልክ እንደዚሁ በዐረብኛ የተነገረ ፍትህ ሲሆን አወረድነው:: እውቀቱ ከመጣልህም በኋላ ዝንባሌዎቻቸውን ብትከተል ከአላህ ቅጣት ወዳጅም ሆነ ጠባቂ ምንም የለህም::
(38) 38. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ካንተ በፊት ብዙ መልዕክተኞችን በእርግጥ ልከናል:: ለእነርሱም ሚስቶችንና ልጆችን አድርገናል:: ማንኛዉም መልዕክተኛ በአላህ ፈቃድ እንጂ ተዓምር ሊያመጣ አይገባዉም:: ለየጊዜው ሁሉ ጽሑፍ አለው::
(39) 39. አላህ የሚፈልገውን ያብሳል:: የሚሻውን ያጸድቃል:: የመጽሐፉ ዋና መሠረትም እርሱ ዘንድ ብቻ ነው::
(40) 40. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የዚያን ያስፈራራናቸውን ቅጣት ከፊሉን በሕይወት እያለህ ብናሳይህ መልካም ነው:: ወይም ሳናሳይህ ብንገድልህ ወቀሳ የለብህም:: ባንተ ላይ ያለብህ መልዕክትህን ማድረስ ብቻ ነው:: ምርመራው ግን በእኛ ላይ ነው::
(41) 41. እኛ ምድርን ከጫፎችዋ የምናጎድላት ሆነን የምናመጣባት መሆናችንን አላወቁምን? አላህም ይፈርዳል:: ለፍርዱም በይግባኝ ገልባጭ የለዉም:: እርሱም ምርመራው ፈጣን ነው::
(42) 42. እነዚያም ከእነርሱ በፊት የነበሩት ሰዎች መከሩ (አሴሩ):: አዘንግቶም የመያዙ ዘዴ በሙሉ የአላህ ብቻ ነው:: አላህ ነፍስ ሁሉ የምትሰራውን ያውቃል:: ከሓዲያን የመጨረሻይቱ አገር ለማን እንደምትሆን ወደፊት ያውቃሉ::
(43) 43. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «እነዚያም በአላህ የካዱ ሰዎች መልእክተኛ አይደለህም።» ይላሉ። «በእኔና በእናንተ መካከል መስካሪ በአላህና እርሱ ዘንድ የመጽሐፉ እውቀት ባለው ሰው በቃ።» በላቸው።