93 - Ad-Dhuhaa ()

|

(1) በረፋዱም፤ (እምላለሁ)

(2) 2. በሌሊትም ጸጥ ባለ ጊዜ እምላለሁ::

(3) 3. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጌታህ አላሰናበተህም፤ አልጠላህምም::

(4) የመጨረሻይቱ ዓለም ከመጀመሪያይቱም ይልቅ ላንተ በላጭ ናት::

(5) ጌታህም ወደ ፊት ብዙ ስጦታ በእርግጥ ይሰጥሃል። ትደሰታለህም።

(6) 6. የቲም ሆነህ አላገኘህምና አላስጠጋህምን? (አስጠግቶሃል)::

(7) 7. የሳትክም ሆነህ አገኘህና መራህ::

(8) 8. ደሃም ሆነህ አገኘህና አከበረህ::

(9) 9. እናም የቲምን አትጨቁን::

(10) 10. ለማኝንም አትገላምጥ::

(11) 11. የጌታህንም ጸጋ ግለጽ::