57 - Al-Hadid ()

|

(1) 1. በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉ ሁሉ አላህን አጠሩ። እርሱም ኃያሉና ጥበበኛው ነው።

(2) 2. የሰማያትና የምድር ንግስና የእርሱው ብቻ ነው:: ሕይወትን የሚሰጥና ሕይወትን የሚነሳ እሱው ብቻ ነው:: እርሱ ሁሉንም ነገር ቻይ ነውና::

(3) 3. እርሱ ( ከበፊቱ ምንም ያልቀደመው) የመጀመሪያ! (ፊት ያለ) (ከኋላው ምንም የሌለ የመጨረሻ) ብቻዉን ቀሪ፤ ከበላዩ ማንም የሌለ (ግልጽና የበላይ) ስውርም (ድብቅ) ነው:: እርሱ (በምድርም ሆነ በሰማይ ያለን) ሁሉ ነገር አዋቂ ነው::

(4) 4. እርሱ ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀናት ብቻ የፈጠረ ነው:: ከዚያ በዐርሹ ላይ ከፍ አለ። ወደ ምድር የሚገባውንና ከእርሷ የሚወጣውን ያውቃል:: ከሰማይ የሚወረደውንና ወደ እርሷ የሚወጣውን ያውቃል:: እርሱ የትም ብትሆኑ (በእውቀቱ) ከናንተው ጋር ነው:: አላህ የምትሰሩትን ሁሉ ተመልካች ነውና::

(5) 5. የሰማያትና የምድር ንግስና የእርሱ ብቻ ነው:: ነገሮች ሁሉ ወደ አላህ ይመለሳሉ::

(6) 6. ሌሊትን በቀን ውስጥ ያስገባል:: ቀንንም በሌሊት ውስጥ ያስገባል:: እርሱም በልቦች ውስጥ የተደበቁትን ሁሉ አዋቂ ነው::

(7) 7. (ሰዎች ሆይ!) በአላህና በመልዕክተኛው እመኑ:: አላህ በእርሱ ላይ ተተካኪዎች ካደረጋችሁ ገንዘብ ዉስጥም ለግሱ:: እነዚያ ከእናንተ መካከል በአላህ ያመኑትና የለገሱት ሁሉ ለእነርሱ ታላቅ ምንዳ አለላቸው::

(8) 8. (ሰዎች ሆይ!) ጌታችሁም ቃልኪዳናችሁን የያዘባችሁ ሲሆን መልዕክተኛውም በጌታችሁ እንድታምኑ የሚጠራችሁ ሲሆን በአላህ የማታምኑበት ምን ምክኒያት አላችሁ? እናንተ በትክክል የምታምኑ ከሆናችሁ?

(9) 9. እርሱ ከጨለማዎች ወደ ብርሀን ሊያወጣችሁ ግልፆች የሆኑን አናቅጽ በባሪያው ላይ የሚያወርድ ነው:: አላህ ለእናንተ በእርግጥ ሩህሩህ አዛኝ ነው::

(10) 10. የሰማያትና የምድር ውርስ ለአላህ ብቻ ሲሆን በአላህ መንገድ የማትለግሱበት ምን ምክንያት አላችሁ? ከናንተ መካከል ከመካ መከፈት በፊት የለገሰና የተጋደለ ሰው ከተከፈተ በኋላ ከለገሰና ከተጋደለ ሰው ጋር አይስተከከልም:: ከእነዚያ በኋላ ከለገሱትና ከተጋደሉት እነዚህ በደረጃ በጣም የላቁ ናቸውና:: ሁሉንም አላህ የመልካሚቱን ተስፋ ቃል ገብቶላቸዋል:: አላህ በምትሰሩት ሁሉ ውስጠ አዋቂ ነው::

(11) 11. ያ ለአላህ መልካም ብድርን የሚያበድርና ለእርሱ አላህ ምንዳውን የሚያነባብርለት ሰው ማን ነው? ለእርሱም መልካም ምንዳ አለው::

(12) 12. ወንድ ትክክለኛ አማኞችንና ሴት ትክክለኛ አማኞችን በስተፊቶቻቸው በቀኞቻቸዉም ብርሀናቸው የሚሮጥ ሲሆን በምታያቸው ቀን (ታላቅ ምንዳ አለላቸው።) "ዛሬ ብስራታችሁ በውስጦቻቸው ዘውታሪዎች ስትኾኑ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈስሱባቸው ገነቶች ናቸው (ይባላሉ)፡፡ ይህ እርሱ ታላቅ እድል ነው::

(13) 13. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የወንድ አስመሳዮችና የሴት አስመሳዮች ለእነዚያ በአላህ ላመኑት "ጠብቁን ከብርሀናችሁ እናበራለንና" የሚሉበትን ቀን አስታውስ:: "ወደ ኋላችሁ ተመለሱ:: ብርሀንንም እዚያው ፈልጉ" ይባላሉ:: በመካከላቸዉም ለእርሱ ደጃፍ ባለው አጥር ይከለላል:: ግቢው በውስጡ ገነት ያለበት ከውጪዉም በኩሉ ደግሞ የእሳት (ስቃይ) ያለበት የሆነ (ደጃፍ ባለው አጥር ይከለላል)

(14) 14. "ከናንተ ጋር አልነበርንምን?" በማለት ይጠሯቸዋል:: "እውነት ነው እኛ ጋር ነበራችሁ:: ግን እናንተ ነፍሶቻችሁን አጠፋችሁ:: በነብዩ አደጋዎችን ተጠባበቃችሁ ትጠራጠራላችሁም:: የአላህ ትዕዛዝ እስከ መጣ ድረስ ከንቱ ምኞቶች አታለሏችሁ። አታላዩም ሰይጣን በአላህ መታገስ ሸነገላችሁ ይሏቸዋል::

(15) 15. በመሆኑም ዛሬ ከናንተም ሆነ በአላህ ከካዱት ሰዎች የገንዘብ ክፍያ (ቤዛ) አይወሰድም:: መኖሪያችሁ የገሀነም እሳት ብቻ ናት:: እርሷ ተገቢያችሁ ናትና:: የገሀነም እሳት መመለሻነቷ ምን ትከፋም" (ይሏቸዋል)::

(16) 16. ለእነዚያ (በአላህ) ላመኑት ለአላህ ተግሳጽና ከቁርኣንም ለወረደው እውነታ ልቦቻቸው ሊፈሩ፤ እንደነዚያ በፊት መጽሐፍን እንደ ተሰጡትና በእነርሱ ላይ ጊዜ ስለ ረዘመባቸው ልቦቻቸውም እንደ ደረቁባቸው ህዝቦች የማይሆኑበት ጊዜ አልቀረበምን? ከእነርሱም ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው።

(17) 17. (ሰዎች ሆይ!) አላህ ምድርን ከሞተች በኋላ ህያው የሚደርጋት መሆኑን እወቁ። ታውቁም ዘንድ አናቅጽን ለእናንተ በእርግጥ አብራራንላችሁ።

(18) 18. የመጸወቱ ወንዶችና የመጸወቱ ሴቶች ለአላህ መልካምን ብድር ያበደሩ ሁሉ ለእነርሱም ምንዳ ይደራረብላቸዋል:: ለእነርሱም መልካም የተከበረ ምንዳ አለላቸው::

(19) 19. እነዚያ በአላህና በመልዕክተኞቹ ያመኑ ሰዎች እነዚያ እነርሱ በጣም እውነቶኞች በጌታቸዉም ዘንድ መስካሪዎች ናቸው:: ለእነርሱ ምንዳቸውም ብርሀናቸዉም አለላቸው:: እነዚያ (በአላህ) የካዱትና በአናቅጻችን ያስተባበሉ ሰዎች ደግሞ የእሳት ጓዶች ናቸው::

(20) 20. (ሰዎች ሆይ!) ቅርቢቱን ሕይወት ጨዋታና ዛዛታ፤ ማጌጫም፤ በመካከችሁም መፎካከሪያ፤ በገንዘቦችና በልጆችም ብዛት መበላለጫ ብቻ መሆኗን እወቁ:: እርሷ በቃዩ ገበሬዎችን ቡቃያው እንደሚያስደስት ዝናብና ከዚያ በቃዩ እንደሚደርቅና ገርጥቶ እንደሚታየው ከዚም የተሰባበረ እንደሚሆን ብጤ ነው:: በመጨረሻይቱም ዓለም ለአጥፊዎች ብርቱ ቅጣት፤ ለትክክለኛ አማኞች ከአላህ ምህረትና ውዴታ አለ:: የቅርቢቱ ሕይወት እኮ የመታለያ ጥቅም እንጂ ሌላ አይደለችም::

(21) 21. (እናንተ ያመናችሁ ሆይ!) በአላህና በመልዕክተኞች ላመኑት ወደ ተዘጋጀችውና የወርዷ ስፋት እንደ ሰማይና ምድር ወደ ሆነችም ገነት ተሸቀዳደሙ:: ይህ የአላህ ችሮታ ነው:: ለሚፈልገው ሰው ብቻ ይሰጠዋል:: አላህ የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነውና::

(22) 22. በምድርም ሆነ በነፍሶቻችሁ መከራ ማንንም አታጋጥምም ሳንፈጥራት በፊት በመጽሐፍ የተመዘገበች ብትሆን እንጂ:: ይህ በአላህ ላይ ቀላል ነው::

(23) 23. (ይህን ማሳወቃችን) ባመለጣችሁ ጸጋ ላይ እንዳታዝኑና አላህ በሰጣችሁ ነገር (በትዕቢት) እንዳትደሰቱ ነው:: አላህ ኩራተኛንና ጉረኛን ሁሉ አይወድምና::

(24) 24. እነርሱም እነዚያ የሚሰስቱና ሰዎችንም በስስት ላይ የሚያዙ ናቸው:: ከእውነት የሚሸሽ (ሰው) ሁሉ ጉዳቱ ለራሱ ብቻ ነው:: አላህ ተብቃቂ ና ምስጉን ነውና::

(25) 25. መልዕክተኞቻችንን በግልጽ ማስረጃዎች አጠናክረን በእርግጥ ላክን:: ሰዎችም በትክክል ቀጥ እንዲሉ መጽሐፎችንና ሚዛንን ወደ እነርሱ አወረድን:: ብረትንም ከውስጡ ብርቱ ኃይልና ለሰዎችም መጠቃቀሚያዎች ያሉበት ሲሆን አወረድን:: አላህ ሃይማኖትንና መልዕክተኞችን በሩቁ ሆኖ የሚረዳውን (ሰው) ሊያውቅ (ሊገልጽ) አወረደው:: አላህ ብርቱና አሸናፊ ነውና::

(26) 26. ኑህንና ኢብራሂምን በእርግጥ ላክን:: በዘሮቻቸዉም ውስጥ ነብይነትንና መጽሐፍትን አደረግን:: ከእነርሱም መካከል ቅን ሰው አለ:: ከእነርሱም መካከል ብዙዎቹ ግን አመጸኞች ናቸው::

(27) 27. ከዚያም በእነርሱ ፈለጋቸው ላይ መልዕክተኞችን አከታተልን:: የመርየም ልጅን ዒሳንም አስከተልን:: ኢንጂልንም ሰጠነው:: በእነዚያም በተከተሉት ሰዎች ልቦች ውስጥ መለዘብንና እዝነትን አደረግን፤ አዲስ የፈጠሯትንም ምንኩስና በእነርሱ ላይ አልደነገግንም:: ግን የአላህን ውዴታ ለመፈለግ ሲሉ ከራሳቸው ፈጠሯት:: ተገቢ አጠባበቅንም አልጠበቋትም:: ከእነርሱም መካከል በአላህ ላመኑት ምንዳቸውን ሰጠናቸው:: ከእነርሱ ብዙዎቹ ግን አመጸኞች ናቸው::

(28) 28. እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ:: በመልክተኛዉም እመኑ:: ከችሮታው ሁለትን ክፍሎች ይሰጣችኋልና:: ለእናተም የምትሄዱበትን ብርሃን ያደርግላችኋል:: ለእናንተም ወንጀላችሁን ይምራል:: አላህ መሀሪና አዛኝ ነው::

(29) 29. (ይህም) የመጽሐፍ ሰዎች ከአላህ ችሮታ በምንም ላይ የማይችሉ መሆናቸውንና ችሮታዉም አላህ ለሚሻው ሰው ብቻ የሚሰጠው በእርሱ እጅ ብቻ መሆኑን እንዲያውቁ ነው:: አላህ የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው::