(1) 1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ምድር በኃይል መንቀጥቀጧን በተንቀጠቀች ጊዜ፤
(2) 2. ምድርም ሸክሞቿን ባወጣች ጊዜ፤
(3) 3. ሰዉም "ምን ሆነች?" ባለ ጊዜ፤
(4) 4. በዚያ ቀን ወሬዎቿን ትናገራለች::
(5) 5. ጌታህ ለእርሷ አሳውቋታልና፤
(6) 6. በዚያ ቀን ሰዎች ሁሉ ስራዎቻቸውን እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ እንደየስራቸው የተበታተኑ ሆነው ከየመቃብራቸው ወደ መቆሚያው ስፍራ ይመለሳሉ::
(7) 7. የብናኝን ክብደት ያህል መልካም የሰራ ሰው ያገኘዋል::
(8) 8. የብናኝን ክብደት ያህል ክፋት የሰራ ሰውም ያገኘዋል::