99 - Az-Zalzala ()

|

(1) 1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ምድር በኃይል መንቀጥቀጧን በተንቀጠቀች ጊዜ፤

(2) 2. ምድርም ሸክሞቿን ባወጣች ጊዜ፤

(3) 3. ሰዉም "ምን ሆነች?" ባለ ጊዜ፤

(4) 4. በዚያ ቀን ወሬዎቿን ትናገራለች::

(5) 5. ጌታህ ለእርሷ አሳውቋታልና፤

(6) 6. በዚያ ቀን ሰዎች ሁሉ ስራዎቻቸውን እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ እንደየስራቸው የተበታተኑ ሆነው ከየመቃብራቸው ወደ መቆሚያው ስፍራ ይመለሳሉ::

(7) 7. የብናኝን ክብደት ያህል መልካም የሰራ ሰው ያገኘዋል::

(8) 8. የብናኝን ክብደት ያህል ክፋት የሰራ ሰውም ያገኘዋል::