(1) 1. ሓ፤ ሚይም፤
(2) 2. ሁሉን ነገር አብራሪ በሆነው መጽሐፍ እንምላለን::
(3) 3. እኛ ቁርኣኑን በዚያች በተባረከችው ሌሊት ውስጥ አወረድነው:: እኛ አስፈራሪዎች ነበርንና::
(4) 4. በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይለያል::
(5) 5. ከእኛ ዘንድ የሆነ ትዕዛዝ ሲሆን አወረድነው:: እኛ መልዕክተኞችን ላኪዎች ነበርንና::
(6) 6. (መልዕክተኞች) ከጌታህ በሆነው ችሮታ (ተላኩ)። እነሆ እርሱ(አላህ) የሚባለዉን ሁሉ ሰሚና ሁሉን አዋቂ ነውና::
(7) 7. የሰማያት፤ የምድር እና በመካከላቸው ያሉ ነገሮች ሁሉ ጌታ ከሆነው (ተላኩ)። የምታረጋግጡ እንደሆናችሁ (ነገሩ እንዳልነው መሆኑን እወቁ)::
(8) 8. ከእርሱም ሌላ አምላክ የለም። ህያው ያደርጋል። ህይወትም ይነሳል። ጌታችሁ የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው::
(9) 9. በእውነቱ እነርሱ የሚጫወቱ ሲሆኑ በመጠራጠር ውስጥ ናቸው::
(10) 10. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ( ሰዎችን) የሚሸፍን በሆነ ግልጽ ጭስ ሰማይ የምትመጣበትን ቀን ተጠባበቅ::
(11) 11.ሰዎችን ይሸፍናል ይህ አሳማሚ ቅጣት ነው::
(12) 12. ጌታችን ሆይ! ክእኛ ላይ ቅጣቱን ግለጥልን:: እኛ ትክክለኛ አማኞች ነንና (ይላሉ::)
(13) 13. አስረጂ መልዕክተኛ የመጣላቸው እና በአላህ የካዱ ሲሆኑ (ቅጣቱ በወረደ ጊዜ) ለእነርሱ መገሰጽ እንዴት ይኖራቸዋል?
(14) 14. ከዚያም «ከሰው የተስተማረ እብድ ነው» ያሉ ሲሆኑ ከእርሱ ዞሩ።
(15) 15. እኛ ቅጣትን ለጥቂት ጊዜ ገላጮች ነን። እናንተ ግን ወደ ክህደታችሁ በእርግጥ አንደገና ተመላሾች ናችሁ::
(16) 16. ታላቂቱን ብርቱ አያያዝ በምንይዝበት ቀን እኛ ተበቃዮች ነን።
(17) 17. ከእነርሱ በፊት የፈርዖንን ህዝቦች በእርግጥ ሞከርን:: ክቡር መልዕክተኛም መጣላቸው::
(18) 18. «የአላህን ባሮች ወደ እኔ አድርሱ (ለኔ ስጡኝ):: እኔ ለእናንተ ታማኝ መልዕክተኛ ነኝና።
(19) 19. «በአላህም ላይ ላትኮሩ። እኔ ግልጽ የሆነን አስረጂ ያመጣሁላችሁ ነኝና በማለት መጣላቸው።
(20) 20. «እኔ እንዳትወግሩኝ በጌታዬና በጌታችሁ ተጠብቂያለሁ።
(21) 21. «በእኔም ባታምኑ ራቁኝ። ተውኝ።» አለ::
(22) 22. «ቀጥሎም እነዚህ አመጸኞች ህዝቦች ናቸው (አጥፋቸው)።» ሲል ጌታውን ለመነ።
(23) 23. (ጌታዉም አለ) «ባሮቼንም ይዘህ በሌሊት ሂድ። እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና።
(24) 24. «ባህሩንም የተከፈተ ሆኖ ተወው፤ እነርሱ የሚሰምጡ ሰራዊት ናቸውና» አለው።
(25) 25. ከአትክልቶችና ከምንጮች ብዙ ነገሮችን ትተው ሄዱ።
(26) 26. ከአዝመራዎችም ከመልካም መቀመጫም
(27) 27. በእርሷ ተደሳቾች ከነበሩባትም ድሎት (ብዙን ነገር ትተው ሞቱ)።
(28) 28. ነገሩ ልክ እንደዚህ ሆነ፤ ለሌሎች ህዝቦች አወረስናትም።
(29) 29. ሰማይና ምድር በእነርሱ ላይ አላለቀሱም:: የሚቆዩም አልነበሩም::
(30) 30. የኢስራኢል ልጆችን ከዚያ አዋራጅ ከሆነው ስቃይ በእርግጥ አዳንናቸው::
(31) 31. ከፈርዖን እርሱ (ፈርዖውን) የኮራ ከወሰን አላፊዎችም አንዱ ነበርና::
(32) 32. ከማወቅም ጋር ከዓለም ህዝቦች መካከል በእርግጥ መረጥናቸው::
(33) 33. ከተአምራቶችም በውስጡ ግልጽ የሆነ ፈተና ያለበትን ሰጠናቸው::
(34) 34. እነዚህ (የመካ ካሓዲያን) በእርግጥ ይላሉ:
(35) 35. «እርሷ የፊተኛይቱ ሞታችን እንጅ (ሌላ) አይደለችም። እኛም የምንቀሰቀስ አይደለንም።
(36) 36. «እውነተኞችም እንደሆናችሁ አባቶቻችንን እስቲ አምጡልን።» (ይላሉ)
(37) 37. እነርሱ በላጮች ናቸውን? ወይስ የቱበዕ ህዝቦችና እነዚያ ከእነርሱ በፊት የነበሩት? እነርሱን አጠፋናቸው። እነርሱ አመጸኞች ነበሩ።
(38) 38. ሰማያትና ምድርን በሁለቱ መካከል ያለውንም ሁሉ ቀላጆች ሆነን አልፈጠርንም::
(39) 39. ሁለቱንም በቁምነገር እንጂ አልፈጠርናቸዉም:: ግን አብዛሀኞቻቸው አያውቀዉም::
(40) 40. የመለያው ቀን ለሁሉም ቀጠሯቸው ነው::
(41) 41. ዘመድ ከዘመዱ ምንንም የማይጠቅምበት እነርሱም የማይረዱበት ቀን ነው::
(42) 42. አላህ ያዘነለትና ያመነ ብቻ ሲቀር:: (እርሱ ይረዳል) እርሱ (አላህ) ሁሉን አሸናፊና አዛኝ ነውና::
(43) 43. የዘቁም ዛፍ
(44) 44. የኃጢአተኞች ምግብ ናት::
(45) 45. እሱም ልክ እንደ ዘይት አተላ በሆዶች ውስጥ ይፈላል።
(46) 46. እንደገነፈለ ውሃ አፈላል የሚፈላ ነው::
(47) 47. ያዙትና ወደ ገሀነም መካከል (ውስጥ) በሀይል ጎትቱት (ገፍትሩት)::
(48) 48. ከዚያም በራሱ ላይ ከፈላ ውሃ ስቃይ አንቧቡበት::
(49) 49. (ይባላልም) «ቅመስ አንተ አሸናፊው፤ ክቡር የነበርክ ነህና።
(50) 50. «ይህ ያ በእርሱ ትጠራጠሩበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)::
(51) 51. ጥንቁቆች በእርግጥ በደህናማ መኖሪያ ውስጥ ናቸው::
(52) 52. በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው::
(53) 53. ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሆነው ከስስ ሐርና ከወፍራም ሐር ይለብሳሉ::
(54) 54. ነገሩ ልክ እንደዚህ ነው። ዓይናማዎች የሆኑን ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን::
(55) 55. በእርሷ ውስጥም የተማመኑ ሆነው ከፍራፍሬ ሁሉ ያዛሉ::
(56) 56. የፊተኛይቱን ሞት እንጂ ዳግመኛ በእርሷ ውስጥ ሞትን አይቀምሱም:: የገሀነምንም ቅጣት አላህ ጠብቋቸዋል።
(57) 57. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) (ይህም ) ከጌታህ (አላህ) የሆነ ትሩፋት ሲሆን ይህም እርሱ ታላቁ እድል ነው::
(58) 58. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቁርኣኑንም በቋንቋህ ያገራነው ህዝቦች ይገነዘቡት ዘንድ ብቻ ነው::
(59) 59. ተጠባበቅ:: እነርሱም ተጠባባቂዎች ናቸውና::