(1) 1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሸፋኝቱ ትንሳኤ ወሬ መጣልህን?
(2) 2. በዚያ ቀን የከሓዲያን ፊቶች ተዋራጆች ናቸው::
(3) 3. ሰሪዎች ለፊዎች ናቸው::
(4) 4. የምታቃጥልን እሳት ይገባሉ::
(5) 5. በጣም ከፈላች ምንጭም ይጋታሉ::
(6) 6. ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃማ) ዛፍ እንጂ ሌላ ምግብ የላቸዉም::
(7) 7. አካልን አያሰባ፤ ከረኃብም አያብቃቃ፤
(8) 8. (የአማንያን) ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው::
(9) 9. በስራቸውም ተደሳቾች ናቸው::
(10) 10. በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው::
(11) 11. በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም::
(12) 12. በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አሉ::
(13) 13. በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አሉ::
(14) 14. በተርታ የተኖሩ ኩባያዎችም፤
(15) 15. የተደረደሩ መከዳዎችም፤
(16) 16. የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አሉ)::
(17) 17. (ከሓዲያን) ግመል እንዴት እንደተፈጠረች አይመለከቱምን?
(18) 18. ሰማይም እንዴት ከፍ እንደተደረገች!
(19) 19. ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!
(20) 20. ምድርም እንዴት እንደተዘረጋች አይመለከቱምን?!
(21) 21. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አስታውስም:: አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና::
(22) 22. በእነርሱ ላይ አስገዳጅ (ተሿሚ) አይደለህም፤
(23) 23. ግን ከእውነት የዞረና የካደ፤
(24) 24. አላህም ከባዱን ቅጣት ይቀጣዋል።
(25) 25. መመለሻቸው ወደ እኛ ብቻ ነው::
(26) 26. ምርመራቸዉም በእኛ ላይ ብቻ ነው::