88 - Al-Ghaashiya ()

|

(1) 1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሸፋኝቱ ትንሳኤ ወሬ መጣልህን?

(2) 2. በዚያ ቀን የከሓዲያን ፊቶች ተዋራጆች ናቸው::

(3) 3. ሰሪዎች ለፊዎች ናቸው::

(4) 4. የምታቃጥልን እሳት ይገባሉ::

(5) 5. በጣም ከፈላች ምንጭም ይጋታሉ::

(6) 6. ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃማ) ዛፍ እንጂ ሌላ ምግብ የላቸዉም::

(7) 7. አካልን አያሰባ፤ ከረኃብም አያብቃቃ፤

(8) 8. (የአማንያን) ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው::

(9) 9. በስራቸውም ተደሳቾች ናቸው::

(10) 10. በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው::

(11) 11. በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም::

(12) 12. በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አሉ::

(13) 13. በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አሉ::

(14) 14. በተርታ የተኖሩ ኩባያዎችም፤

(15) 15. የተደረደሩ መከዳዎችም፤

(16) 16. የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አሉ)::

(17) 17. (ከሓዲያን) ግመል እንዴት እንደተፈጠረች አይመለከቱምን?

(18) 18. ሰማይም እንዴት ከፍ እንደተደረገች!

(19) 19. ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!

(20) 20. ምድርም እንዴት እንደተዘረጋች አይመለከቱምን?!

(21) 21. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አስታውስም:: አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና::

(22) 22. በእነርሱ ላይ አስገዳጅ (ተሿሚ) አይደለህም፤

(23) 23. ግን ከእውነት የዞረና የካደ፤

(24) 24. አላህም ከባዱን ቅጣት ይቀጣዋል።

(25) 25. መመለሻቸው ወደ እኛ ብቻ ነው::

(26) 26. ምርመራቸዉም በእኛ ላይ ብቻ ነው::