(1) 1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከአጋንንት የሆኑ ቡድኖች ቁርኣንን አዳመጠው እንዲህ ማለታቸው ተወረደልኝ በል: «እኛ አስደናቂ የሆነን ቁርአን ሰማን፤
(2) 2. «ወደ ቀጥታ መንገድ የሚመራን (ቁርኣን ሰማን) በእርሱም አመንን:: በጌታችን አንድንም አናጋራም::
(3) 3. «እነሆ የጌታችን ክብር ላቀ:: ሚስትንም ልጅንም አልያዘም::
(4) 4. «እነሆ ቂላችን በአላህ ላይ ወሰን ያለፈን ውሸት ይናገር ነበር::
(5) 5. «እኛም ሰዎችና ጋኔኖች በአላህ ላይ ውሸትን ቃል አይናገሩም ማለትን ጠረጠርን» አሉ በማለት ወደእኔ ተወረደ በል።
(6) 6. እነሆ ከሰዎች የሆኑ ወንዶች ከአጋንንት በሆኑ ወንዶች ይጠበቁ ነበር። ኩራትንም (ጥመትን) ጨመሯቸው።
(7) 7. አላህ አንድንም አይቀሰቅስም ማለትን እንደጠረጠራችሁ እነርሱም ጠረጠሩ::
(8) 8. እኛም ሰማይን ለመድረስ ፈለግን ብርቱ ጠባቂዎችንና ችቦዎችንም ተሞልታ አገኘናት::
(9) 9. እኛም ከእርሷ ወሬን ለማዳመጥ በመቀመጫዎች እንቀመጥ ነበር:: አሁን (ግን) የሚያዳምጥ (ሁሉ) ተጠባባቂ የእሳት ችቦ ያገኘዋል።
(10) 10. እኛም በምድር ውስጥ ባሉት ክፉ ተሽቷል? ወይስ በእነርሱ (በኩል) ጌታቸው ደግን ነገር ሽቷል? ማለትን አናውቅም።
(11) 11. ከእኛም ውስጥ ደጋጎች አሉ:: ከእኛም ውስጥ ከዚህ ሌላ የሆኑ አሉ:: የተለያዩ መንገዶች ባለቤቶች ነበርን::
(12) 12. እኛም አላህን በምድር ውስጥ ፈጽሞ የማናቅተው ሸሽተንም ፈጽሞ የማናመልጠው መሆናችንን አረጋገጥን::
(13) 13. እኛም መሪውን በሰማን ጊዜ በእርሱ አመንን:: ያ! በጌታው የሚያምን ሰው ሁሉ መጎደልንም ሆነ መጨመርን አይፈራም::
(14) 14. ከእኛም ውስጥ ሙስሊሞች አሉ:: ከእኛም ውስጥ በዳዩች አሉ:: እነዚያ የሰለሙ ሰዎች ቅንን መንገድ መረጡ::
(15) 15. እነዚያ በዳዩችማ ለገሀነም ማገዶ ሆኑ::
(16) 16. (ሰዎች ሁሉ በአላህ) በመንገድ ላይ ቀጥ ባሉ ኖሮ ብዙ ዝናብን ባጠጣናቸው ነበር::
(17) 17. በእርሱ ልንፈትናቸው (ባጠጣናቸው ነበር)። ያ ጌታውን ከማስታወስ የሚያፈገፍግ ሰው አስቸጋሪ ቅጣት ውስጥ ያስገባዋል::
(18) 18. መስጊዶች ሁሉ የአላህ ብቻ ናቸው:: እናም በውስጣቸው ከአላህ ጋር አንድንም አትገዙ ማለትን ተወረደልኝ::
(19) 19. እነሆ የአላህ ባሪያ (ሙሐመድ) አላህን የሚጠራው ሆኖ በተነሳ ጊዜ ጋኒኖቹ በእርሱ ላይ ድርብርቦች ሊሆኑ ቀረቡ::
(20) 20. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «እኔ የማመልከው ጌታየን ብቻ ነው:: በእርሱ አንድንም አላጋራም» በል።
(21) 21. «እኔ ለእናንተ ጉዳትንም ሆነ ማቅናትን አልችልም» በል።
(22) 22. «እኔን ከአላህ ቅጣት አንድም (አካል) አያድነኝም:: ከእርሱ ሌላ መጠጊያም አላገኝም» በል።
(23) 23. ከአላህ የሆኑ መልዕክቶችን ከማድረስ በስተቀር አልችልም:: አላህንና መልዕክተኛውን የሚያምጽ ሁሉ ለእርሱ የገሀነም እሳት አለው:: በውስጧም ዘላለም ዘውታሪዎች ሲሆኑ።
(24) 24. የሚስፈራሩበትንም ባዩ ጊዜ ረዳተ ደካማ ቁጥሩም አነስተኛ የሆነው ማን እንደሆነ በእርግጥ ያውቃሉ::
(25) 25. «ያ! የምትስፈራሩበት ነገር ቅርብ ወይም ጌታየ ለእርሱ የተወሰነ ጊዜን የሚያደርግለት እሩቅ መሆኑን አላውቅም።» በላቸው
(26) 26. እርሱም እሩቁን ሚስጢር አዋቂ ነው::በምስጢሩም ላይ አንድንም አያሳውቅም፡፡»
(27) 27. (በሚስጢሩም ላይ) ከመልዕክተኛው ለወደደው ቢሆን እንጂ (ለሌላ አንድንም አያሳውቅም):: አይገልጽም:: ለእርሱም ከበስተፊቱም ከበስተኋላዉም ጠባቂዎቸን ያደርግለታል::
(28) 28. ከእነርሱ ዘንድ ባለው ነገር እውቀት የከበበና ነገሩንም ሁሉ በቁጥር ያጠቃለለ ሲሆን የጌታቸውን መልዕክቶች ያደረሱ መሆናቸውን ያውቅ (ዘንድ ጠባቂ ያደርጋል)::