78 - An-Naba ()

|

(1) 1. ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?

(2) 2. ከታላቁ ዜና (ቁርኣን) ይጠያየቃሉ።

(3) 3. ስለዚያ እነርሱ በእርሱ ላይ ስለተለያዩበት (ስለተወዛገቡበት)::

(4) 4. ጉዳዩ እነርሱ እንደሚሉት አይደለም:: (ትክክለኛውን) ወደ ፊት ያውቃሉ::

(5) 5. ከዚያም ይከልከሉ፤ (ትክክለኛውን) ወደ ፊት ያውቃሉ።

(6) 6. ምድርን ምንጣፍ አላደርግንምን?

(7) 7. ጋራዎችንም ችካሎች (አላደረግንምን)?

(8) 8. ጥንዶች አድርገንም ፈጠርናችሁ።

(9) 9. እንቅልፋችሁንም እረፍት አደረግን።

(10) 10. ሌሊቱንም ልባስ አደረግን::

(11) 11. ቀኑንም ለኑሮ መስሪያ (ለጉዳይ መከወኛ) አደረግን።

(12) 12. ከበላያቸሁም ሰባት ብርቱዎችን (ሰማያት) ገነባን።

(13) 13. አንጸባራቂ ብርሃንንም አደርግንላችሁ።

(14) 14. ከአረገዙት ደመናዎችም የሚንቧቧ ውሃን አወረድን::

(15) 15.በእርሱ እህልንና ቅጠላ ቅጠልን፤ እናወጣ ዘንድ(አወረድን)

(16) 16. የተቆላለፉ አትክልቶችንም ::

(17) 17. (በህዝቦች መካከልም) የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው።

(18) 18. (ይሀዉም) በቀንዱ በሚነፋበትና በቡድን በቡድን ሆናችሁም በምትመጡበት ቀን ነው።

(19) 19. ሰማይም በምትከፈትና ባለ ብዙ ደጃፎችም በምትሆንበት ቀን፤

(20) 20. ጋራዎችም በሚናዱበትና እንደ ሲሪብዶም በሚሆንበትም ቀን ነው።

(21) 21. ገሀነም (ለከሓዲያን) መጠባበቂያ ኬላ (ስፍራ) ናት::

(22) 22. ለህግ ተላላፊዎች መመላለሻ ስትሆን።

(23) 23. በውስጧ ብዙ ዘመናትን ነዋሪዎች ሲሆኑ፤

(24) 24. በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጠንም አይቀምሱም (አያገኙም)

(25) 25. ሙቅ የፈላ ውሃንና እዥን እንጂ

(26) 26. ተመጣጣኝን ምንዳ ይመነዳሉ።

(27) 27. ምርመራ (እንዳለባቸው) ቅንጣት አይጠብቁም ነበርና።

(28) 28. በአናቅጻችንም ማስተባበልን አስተባበሉ።

(29) 29. ነገሩን ሁሉ የተፃፈ ሲሆን አጠቃለልነው።

(30) 30. «(የጃችሁን) ቅመሱም፤ ቅጣትን እንጂ ሌላን አንጨምርላችሁም» (ይባላሉም)

(31) 31. ለጥንቅቆቹ (አላህን ለሚፈሩ) ስኬት አላቸው።

(32) 32. አትክልቶችና ወይኖችም፤

(33) 33. በእድሜ እኩያዎች የሆኑ ጡተ ጉችማዎችም፤

(34) 34. የተሞሉ ብርጭቆዎችም፤

(35) 35. በውስጧ ትርፍ ቃልንም፤ ማስዋሸትንም አይሰሙም::

(36) 36. ከጌታህ የሆነን ምንዳ፤ በቂ ስጦታን ተሰጡ::

(37) 37. የሰማያትና የምድር በመካከላቸዉም ላለው ሁሉ ጌታ ከሆነውና በጣም አዛኝ ከሆነው ተመነዱ፤ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም::

(38) 38. መልአኩ (ጅብሪል) እና ሌሎች መላዕክትም የተሰለፉ ሆነው በሚቆሙበት ቀን አረህማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ብቻ ቢሆን እንጂ መነጋገርን አይችሉም።

(39) 39. ያ! የእውነት ቀን ነው። የፈለገ ሰው ወደ ጌታው በመልካም ተግባር መመለስን ተግባሩ አድርጎ ይይዛል።

(40) 40. እኛ ቅርብ የሆነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ። ሰዎች ሁሉ በሁለት እጆቻቸው ያስቀደሙትን በግልጽ የሚያይበትና ከሓዲያን ሁሉ «ዋ ምኞቴ! ምንነው አፈር በሆንኩ ባልተቀሰቀስኩኝ» የሚሉበት ቀን።