(1) 1. በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ አላህን አጠራ:: እርሱም ሁሉንም አሸናፊና ጥበበኛው ነው::
(2) 2. እርሱ ያ! ከመጽሐፍ ሰዎች መካከል እነዚያን በአላህ የካዱትን ወገኖች ከቤቶቻቸው የመጀመሪያውን ማስወጣት ያስወጣቸው ነው:: (ሙስሊሞች ሆይ!) መውጣታቸውንም አላሰባችሁትም ነበር:: እነርሱም ምሽጎቻቸው ከአላህ ኃይል የሚከላከሉላቸው መሆናቸውን አሰቡ:: አላህ ግን ካላሰቡት በኩል መጣባቸው:: እናም በልቦቻቸው ውስጥ መርበድበድን (ፍርሃትን) ጣለባቸው:: ቤቶቻቸውን በገዛ እጆቻቸውና በትክክለኛ አማኞች እጅ ያፈርሳሉ (አፈረሱ):: እናንተ የአእምሮ ባለቤቶች ሆይ! አስተውሉ::
(3) 3. በእነርሱም ላይ አላህ ከአገር መውጣትን ባልፈረደ ኖሮ በቅርቢቱ ዓለም በቀጣቸው ነበር:: ለእነርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም የእሳት ቅጣት አለባቸው::
(4) 4. ይህ እነርሱ አላህንና መልዕክተኛውን በመከራከራቸው ምክንያት ነው:: አላህን የሚከራከር ሰው ሁሉ (ይቀጣዋል።) አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና ይቀጣቸዋል::
(5) 5. ከዘንባባ (ከተምር ዛፍ) ማንኛዋም የቆረጣችኋት ወይም በግንዶቿ ላይ የቆመች ሆና የተዋችኋት ሁሉ በአላህ ፈቃድ ነው:: አመጸኞችንም ያዋርድ ዘንድ (መቁረጥን ፈቀደ)::
(6) 6. ከእነርሱም ገንዘብ ወደ መልዕክተኛው አላህ የመለሰውን በእርሱ ላይ ፈረሶችንና ግመሎችን አላስጋልባችሁበትም:: ግን አላህ መልዕክተኞቹን በሚሻው ላይ ይሾማል:: አላህ በሁሉ ነገር ላይ ቻይ ነውና::
(7) 7. አላህ ከከተሞች ሰዎች ሀብት መካከል በመልዕክተኛው ላይ የመለሰው ሀብት ከናንተ ውስጥ በሀብታሞች መካከል ብቻ ተዘዋዋሪ እንዳይሆን ለአላህና ለመልዕክተኛው፤ ለዝምድና ባለቤትም፤ አባት ለሌላቸው የቲም ልጆችም፤ ለድሆችና፤ ለመንገደኛ፤ የሚሰጥ ነው:: መልዕክተኛው የሰጣችሁን ሁሉ ማንኛዉም ነገር ያዙት:: የከለከላችሁን ነገር ሁሉም ተከልከሉ:: አላህን ፍሩ። አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና::
(8) 8. ለእነዚያ የአላህን ችሮታና ውዴታውን የሚፈልጉና አላህንና መልዕክተኛውን የሚረዱ ሆነው ከአገሮቻቸውና ከገንዘቦቻቸው ለተወጡ (ለተባረሩ) ስደተኞች ድሆች ይሰጣል:: እነዚያ እነርሱ እውነተኞች ናቸው::
(9) 9..እነዚያ ከበፊታቸው ሀገሪቱን መዲና መኖሪያ ያደረጓትና እምነት በልባቸው የሰረጸባቸው ወደ እነርሱ የተሰደዱትን ሰዎች ይወዳሉ:: ስደተኞችም ከተሰጡት ነገር ላይ በልቦቻቸው ውስጥ እንኳን ምንም ቅሬታን አያሳድሩም:: በእነርሱ ላይ ችግር ቢኖርባቸዉም እንኳ በነፍሶቻቸው ላይ ሌላውን ያስቀድማሉ:: ከነፍሶቻቸው ንፉግነት የሚጠበቁ ሰዎች ሁሉ እነዚያ የተሳካለቸውና ምኞታቸውን አግኚዎች ማለት እነርሱ ብቻ ናቸው::
(10) 10. እነዚያ ከበኋላቸው የመጡት «ጌታችን ሆይ! ለእኛም ለእነዚያም በእምነት ለቀደሙን ወንድሞቻችንም ምህረት አድርግ:: በልቦቻችንም ውስጥ ለእነዚያ ለአመኑት ሰዎች ሁሉ ጥላቻን አታድርግ:: ጌታችን ሆይ! አንተ ሩህሩህ፤ አዛኝ ነህና» ይላሉ።
(11) 11. እነዚያን ወደ ንፍቅና የገቡትን አላወክምን? ከመጽሐፍ ሰዎች መካከል ለእነዚያ ለካዱት ወንድሞቻቸው «ከአገር ብትባርሩ አብረናችሁ እንወጣለን:: በእናንተ ጉዳይ አንድንም ሰው በፍጹም ሁልጊዜም አንታዘዝም:: ጦርነት ቢታወጅባችሁም በእርግጥ እንረዳችኋለን» ይሏቸዋል:: አላህም እነርሱ ውሸታሞች መሆናቸውን ይመሰክራል::
(12) 12. ቢባረሩም አብረዋቸው አይባረሩም:: ቢገደሉም (ቢወጉም) ቢዘመትባቸዉም አይረዱዋቸዉም:: ቢረዷቸዉም ለሽሽት ጀርባዎችን ያዞራሉ:: ከዚያም እርዳታን አያገኙም::
(13) 13. (እናንተ ያመናችሁ ሆይ!) እናንተ በልቦቻቸው ውስጥ በማስፈራራት ከአላህ ይልቅ የበረታችሁ (የከበዳችሁ) ናችሁ:: ይህም የሆነው እነርሱ የማይገነዘቡ ህዝቦች በመሆናቸው ነው::
(14) 14. በተመሸጉ ከተሞች ውስጥ ወይም ከአጥሮች በስተጀርባ ሆነው እንጂ የተሰበሰቡ ሆነው አይዋጓችሁም:: ኃይላቸው በመካከላቸው ብርቱ ነው:: ልቦቻቸው የተበታተኑ ሲሆን የተሰበሰቡ ናቸው ብለህ ትጠራጠራቸዋለህ (አንድ ይመስሉሃል):: ይህ እነርሱ አእምሮ የሌላቸው ህዝቦች በመሆናቸው ነው::
(15) 15. ብጤያቸው ልክ እንደነዚያ ከእነርሱ በፊት በቅርብ ጊዜ የተግባራቸውን ቅጣት እንደቀመሱት ወገኖች ብጤ ነው:: ለእነርሱም አሳማሚ ቅጣት አለባቸው::
(16) 16. ምሳሌያቸው ልክ እንደዚያ ሰውን «በአላህ ካድ ብሎ ሰውየው በካደ ጊዜ እኔ ካንተ ንጹህ ነኝ እኔ የዓለማትን ጌታ አላህን እፈራለሁ» እንዳለው ሰይጣን ነው።
(17) 17. የሁለቱም መጨረሻቸው እነርሱ በውስጡ ዘወታሪዎች ሲሆኑ በእሳት ውስጥ መሆን ነው:: ይህም ቅጣት የበዳዩች ሁሉ ዋጋ ነው::
(18) 18. እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን በትክክል ፍሩ:: ማንኛይቱም ነፍስ ለነገ ያስቀደመችውን ትመልከት፤ አላህን በትክክል ፍሩ:: አላህ በምትሰሩት ነገር ሁሉ ውስጠ አዋቂ ነውና::
(19) 19. እንደ እነዚያ አላህን እንደረሱትና ነፍሶቻቸውን እንዳስረሳቸው ሰዎች አትሁኑ:: እነዚያ እነርሱ አመጸኞች ናቸው::
(20) 20. የእሳት ጓዶችና የገነት ጓዶች እኩል አይሆኑም:: የገነት ጓዶች ምኞታቸውን አግኝዎች ናቸውና::
(21) 21. (ሙሐመድ ሆይ)፤ ይህንን ቁርኣን በተራራ ላይ ባወረድነው ኖሮ ከአላህ ፍራቻ የተነሳ ተዋራጅና ተሰንጣቂ ሆኖ ባየኸው ነበር:: እነዚህን ምሳሌዎች ለሰዎች ያስተነትኑ ዘንድ እንገልፃቸዋለን::
(22) 22. እርሱ ያ አላህ ነው:: ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የሌለ፤ ሩቁንና ቅርቡን አዋቂ የሆነ ነው:: እርሱ እጅግ በጣም ሩህሩህ፤ በጣም አዛኝ ነው::
(23) 23. እርሱ ያ አላህ ነው:: ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የሌለ፤ ንጉሱ፤ ከጎደሎ ሁሉ የጠራ፤ የሰላም ባለቤት፤ ጸጥታን ሰጪ፤ ባሮቹን ጠባቂ፤ አሸናፊ፤ ኃያልና ኩሩ ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው::
(24) 24. እርሱ አላህ ፈጣሪዉ፤ ከኢምንት አስገኚዉና ቅርጽን አሳማሪው ነው:: ለእርሱ መልካሞች ስሞች አሉት:: በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ እርሱን ያሞግሳል:: እርሱም ሁሉን አሸናፊና ጥበበኛ ነው::