(1) 1. በበለስና፤ በወይራ ዛፍ እምላለሁ፣
(2) 2. በሲና ተራራም፤
(3) 3. በዚህ በጸጥተኛው (ጸጥታ በነገሰበት) አገር መካም እምላለሁ።
(4) 4. በርግጥ ሰውን በጣም በአማረ አቋም ላይ ፈጠርነው::
(5) 5. ከዚያም (ከፊሉን) ከበታቾች ሁሉ በታች አድርገን መለስነው::
(6) 6. እነዚያ በአላህ ያመኑትና መልካም ተግባራት የሰሩት ሲቀሩ ለእነርሱማ የማይቋረጥ ምንዳ አለላቸው::
(7) 7. (የሰው ልጅ ሆይ) ታዲያ ከዚህ (እውነታ) በኋላ በፍርዱ ምን አስተባባይ አደረገህ?
(8) 8. አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ ፈራጅ አይደለምን?